83. سورة المطففين - ቁርዓን
- 1. ለሰላቢዎች ወዮላቸው፡፡
- 2. ለእነዚያ ከሰዎች ባስሰፈሩ ጊዜ የሚያስሞሉ፡፡
- 3. ለእነርሱም (ለሰዎቹ) በሰፈሩ ወይም በመዘኑላቸው ጊዜ የሚያጎድሉ (ለኾኑት)፡፡
- 4. እነዚያ እነርሱ ተቀስቃሾች መኾናቸውን አያውቁምን?
- 5. በታላቁ ቀን፡፡
- 6. ሰዎች ሁሉ ለዓለማት ጌታ (ፍርድ)፤ በሚቆሙበት ቀን (ተቀስቃሾች መኾናቸውን)፡፡
- 7. በእውነት የከሓዲዎቹ (የሰላቢዎቹ) መጽሐፍ በእርግጥ በሲጂን ውስጥ ነው፡፡
- 8. ሲጂንም ምን እንደ ኾነ ምን አሳወቀህ?
- 9. የታተመ መጽሐፍ ነው፡፡
- 10. ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡