89. سورة الفجر - ቁርዓን
- 1. በጎህ እምላለሁ፡፡
- 2. በዐሥር ሌሊቶችም፡፡
- 3. በጥንዱም በነጠላውም፡፡
- 4. በሌሊቱም በሚኼድ ጊዜ፡፡
- 5. በዚህ (መሓላ) ለባለ አእምሮ ታላቅ መሓላ አለበትን?
- 6. ጌታህ በዓድ እንዴት እንደ ሠራ አታውቅምን?
- 7. በኢረም በባለ ረዣዢሚቱ አዕማድ፡፡
- 8. በዚያች ብጤዋ በአገሮች ውስጥ ያልተፈጠረ በኾነችው፡፡
- 9. በሰሙድም በእነዚያ በሸለቆው ቋጥኝን የቆረጡ በኾኑት፡፡
- 10. በፈርዖንም ባለ ችካሎች በኾነው፡፡