85. سورة البروج - ቁርዓን
- 1. የቡርጆች ባለቤት በኾነችው ሰማይ እምላለሁ፡፡
- 2. በተቀጠረው ቀንም፤
- 3. በተጣጅና በሚጣዱትም፤ (እምላለሁ)፡፡
- 4. የጉድቡ ባለቤቶች ተረገሙ፡፡
- 5. የማገዶ ባለቤት የኾነቺው እሳት (ባለቤቶች)፡፡
- 6. እነርሱ በርሷ (አፋፍ) ላይ ተቀማጮች በኾኑ ጊዜ፤ (ተረገሙ)፡፡
- 7. እነርሱም በምእምናኖቹ በሚሠሩት (ማሰቃየት) ላይ መስካሪዎች ናቸው፡፡
- 8. ከእነርሱም በአላህ አሸናፊው፣ ምስጉኑ በኾነው (ጌታ) ማመናቸውን እንጅ ሌላ ምንም አልጠሉም፡፡
- 9. በእዚያ የሰማያትና የምድር ንግሥና ለእርሱ ብቻ በኾነው (አላህ ማመናቸውን)፡፡ አላህም በነገሩ ሁሉ ላይ መስካሪ ነው፡፡