77. سورة المرسلات - ቁርዓን
- 1. ተከታታይ ኾነው በተላኩት፣
- 2. በኀይል መንፈስን ነፋሾች በኾኑትም፣
- 3. መበተንን በታኞች በኾኑትም፤ (ነፋሶች)፣
- 4. መለየትን ለይዎች በኾኑትም፣
- 5. መገሠጫን (ወደ ነቢያት) ጣይዎች በኾኑትም፣
- 6. ምክንያትን ለማስወገድ ወይም ለማስፈራራት (ጣይዎች በኾኑት መላእክት) እምላለሁ፡፡
- 7. ያ የምትስፈራሩበት (ትንሣኤ) በእርግጥ ኋኝ ነው፡፡
- 8. ከዋክብትም (ብርሃንዋ) በታበሰች ጊዜ፡፡
- 9. ሰማይም በተከፈተች ጊዜ፡፡
- 10. ጋራዎችም በተንኮተኮቱ ጊዜ፡፡