سورة المرسلات - ቁርኣን - ሃሩን ያህያ
-
1. ተከታታይ ኾነው በተላኩት፣
-
2. በኀይል መንፈስን ነፋሾች በኾኑትም፣
-
3. መበተንን በታኞች በኾኑትም፤ (ነፋሶች)፣
-
4. መለየትን ለይዎች በኾኑትም፣
-
5. መገሠጫን (ወደ ነቢያት) ጣይዎች በኾኑትም፣
-
6. ምክንያትን ለማስወገድ ወይም ለማስፈራራት (ጣይዎች በኾኑት መላእክት) እምላለሁ፡፡
-
7. ያ የምትስፈራሩበት (ትንሣኤ) በእርግጥ ኋኝ ነው፡፡
-
8. ከዋክብትም (ብርሃንዋ) በታበሰች ጊዜ፡፡
-
9. ሰማይም በተከፈተች ጊዜ፡፡
-
10. ጋራዎችም በተንኮተኮቱ ጊዜ፡፡
-
11. መልክተኞቹም ወቅት በተደረገላቸው ጊዜ፡፡
-
12. ለየትኛው ቀን ተቀጠሩ (የሚባል ሲኾን)፤
-
13. ለመለያው ቀን (በተባለ ጊዜ፤ በፍጡሮች መካከል ይፈረዳል)፡፡
-
14. የመለያውም ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?
-
15. ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
-
16. የፊተኞቹን (ሕዝቦች) አላጠፋንምን?
-
17. ከዚያም የኋለኞቹን እናስከትላቸዋለን፡፡
-
18. በአመጸኞች ሁሉ እንደዚሁ እንሠራለን፡፡
-
19. ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
-
20. ከደካማ ውሃ አልፈጠርናችሁምን?
-
21. በተጠበቀ መርጊያ ውስጥም (በማሕፀን) አደረግነው፡፡
-
22. እስከ ታወቀ ልክ ድረስ፡፡ መጠንነውም፤ ምን ያማርንም
-
23. መጣኞች ነን!
-
24. ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
-
25. ምድርን ሰብሳቢ አላደረግናትምን?
-
26. ሕያዋን ኾናችሁ ሙታንም ኾናችሁ፡፡
-
27. በውስጧም ከፍተኛዎችን ተራራዎች አደረግን፡፡ ጣፋጭ ውሃንም አጠጣናችሁ፡፡
-
28. ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
-
29. «ወደዚያ በእርሱ ታስተባብሉ ወደ ነበራችሁት (ቅጣት) አዝግሙ፡፡
-
30. «ባለ ሦስት ቅርንጫፎች ወደ ኾነው ጥላ አዝግሙ፤» (ይባላሉ)፡፡
-
31. አጠላይ ያልኾነ ከእሳቱም ላንቃ የማያድን ወደ ኾነው (አዝግሙ)፡፡
-
32. እርሷ እንደ ታላላቅ ሕንጻ የኾኑን ቃንቄዎች ትወረውራለች፡፡
-
33. (ቃንቄውም) ልክ ዳለቻዎች ግመሎችን ይመስላል፡፡
-
34. ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
-
35. ይህ የማይናገሩበት ቀን ነው፡፡
-
36. ይቅርታም ይጠይቁ ዘንድ፤ ለእነርሱ አይፈቀድላቸውም፡፡
-
37. ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
-
38. ይህ መለያው ቀን ነው፡፡ እናንተንም የፊተኞቹንም ሰብሰብናችሁ፡፡
-
39. ለናንተም (ለማምለጥ) ብልሃት እንዳላችሁ ተተናኮሉኝ፡፡
-
40. ላስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
-
41. ጥንቁቆቹ በጥላዎችና በምንጮች ውስጥ ናቸው፡፡
-
42. ከሚከጅሉትም ሁሉ በፍራፍሬዎች ውስጥ ናቸው፡፡
-
43. «ትሠሩት በነበራችሁት ዋጋ የምትደሰቱ ኾናችሁ ብሉ፣ ጠጡም፤» (ይባላሉ)፡፡
-
44. እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡
-
45. ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
-
46. ብሉ፤ ጥቂትንም (ጊዜ) ተጠቀሙ፡፡ እናንተ አመጸኞች ናችሁና፡፡
-
47. ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
-
48. «ለእነርሱ ስገዱም» በተባሉ ጊዜ አይሰግዱም፡፡
-
49. ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
-
50. ከእርሱም ሌላ በየትኛው ንግግር ያምናሉ?
ሼር ያድርጉ
1
ورَةُ الْفَاتِحَة
2
ورَةُ البقرة
3
سُورَةُ آل عمران
4
سورة النساء
5
سورۃ المائدة
6
سورة الأنعام
7
سورة الاعراف
8
سورۃ الانفال
9
سورة التوبة
10
سورة يونس
11
سورۃ ھود
12
سورة يوسف
13
سورة الرعد
14
سورة ابراهيم
15
سورة الحجر
16
سورة النحل
17
سورة الإسراء
18
سورة الكهف
19
سورة مريم
20
سورة طه
21
سورة الأنبياء
22
سورة الحج
23
سورة المؤمنون
24
سورة النور
25
سورة الفرقان
26
سورة الشعراء
27
سورة النمل
28
سورة القصص
29
سورة العنكبوت
30
سورة الروم
31
سورة لقمان
32
سورة السجدة
33
سورة الأحزاب
34
سورة سبإ
35
سورة فاطر
36
سورةيس
37
سورة الصافات
38
سورة ص
39
سورة الزمر
40
سورة غافر
41
سورة فصلت
42
سورة الشورى
43
سورة الزخرف
44
سورة الدخان
45
سورة الجاثية
46
سورة الأحقاف
47
سورة محمد
48
سورة الفتح
49
ورة الحجرات
50
سورة ق
51
سورة الذاريات
52
سورة الطور
53
سورة النجم
54
سورة القمر
55
سورة الرحمن
56
سورة الواقعة
57
سورة الحديد
58
سورة المجادلة
59
سورة الحشر
60
سورة الممتحنة
61
سورة الصف
62
سورة الجمعة
63
سورة المنافقون
64
سورة التغابن
65
سورة الطلاق
66
سورة التحريم
67
سورة الملك
68
سورة القلم
69
سورة الحاقة
70
سورة المعارج
71
سورة نوح
72
سورة الجن
73
سورة المزمل
74
سورة المدثر
75
سورة القيامة
76
سورة الانسان
77
سورة المرسلات
78
سورة النبإ
79
سورة النازعات
80
سورة عبس
81
سورة التكوير
82
سورة الإنفطار
83
سورة المطففين
84
سورة الإنشقاق
85
سورة البروج
86
سورة الطارق
87
سورة الأعلى
88
سورة الغاشية
89
سورة الفجر
90
سورة البلد
91
سورة الشمس
92
سورة الليل
93
سورة الضحى
94
سورة الشرح
95
سورة التين
96
سورة العلق
97
سورة القدر
98
سورة البينة
99
سورة الزلزلة
100
سورة العاديات
101
سورة القارعة
102
Aسورة التكاثر
103
سورة العصر
104
سورة الهمزة
105
سورة الفيل
106
سورة قريش
107
سورة الماعون
108
سورة الكوثر
109
سورة الكافرون
110
سورة النصر
111
سورة المسد
112
سورة الإخلاص
113
سورة الفلق
114
سورة الناس