1. እያለከለኩ ሩዋጮች በኾኑት (ፈረሶች) እምላለሁ፡፡
2. (በሰኮናቸው) እያጋጩ እሳትን አውጪዎች በኾኑትም፤
3. በማለዳ ወራሪዎች በኾኑትም፤
4. በእርሱ አቧራን በቀሰቀሱትም፤
5. በ(ጠላት) ክቢ መካከል በእርሱ (በጧት) በተጋፈጡትም እምላለሁ፡፡
6. ሰው ለጌታው ብርቱ ከሓዲ ነው፡፡
7. እርሱም በዚህ ላይ መስካሪ ነው፡፡
8. እርሱም ገንዘብን ለመውደድ በጣም ብርቱ ነው፡፡
9. (ሰው) አያውቅምን? በመቃብሮች ያሉት (ሙታን) በተቀሰቀሱ ጊዜ፤
11. ጌታቸው በዚያ ቀን በእነርሱ (ነገር) በእርግጥ ውስጠ አዋቂ ነው፡፡