81. سورة التكوير - ቁርዓን
- 1. ፀሐይ በተጠቀለለች ጊዜ፤
- 2. ከዋክብትም በረገፉ ጊዜ፤
- 3. ተራራዎችም በተነዱ ጊዜ፤
- 4. የዐሥር ወር እርጉዞች ግመሎችም (ያለጠባቂ) በተተዉ ጊዜ፤
- 5. እንስሳትም ሁሉ በተሰበሰቡ ጊዜ፤
- 6. ባሕሮችም በተቃጠሉ ጊዜ፤
- 7. ነፍሶችም (በየአካሎቻቸው) በተቆራኙ ጊዜ፤
- 8. በሕይወቷ የተቀበረችውም ሴት ልጅ በተጠየቀች ጊዜ፤
- 9. በምን ወንጀል እንደ ተገደለች፤
- 10. ጽሑፎችም በተዘረጉ ጊዜ፤