88. سورة الغاشية - ቁርዓን
- 1. የሸፋኝቱ (ትንሣኤ) ወሬ መጣህን?
- 2. ፊቶች በዚያ ቀን ተዋራጆች ናቸው፡፡
- 3. ሠሪዎች ለፊዎች ናቸው፡፡
- 4. ተኳሳን እሳት ይገባሉ፡፡
- 5. በጣም ከፈላች ምንጭ ይጋታሉ፡፡
- 6. ለእነርሱ ዶሪዕ ከሚባል (እሾሃም) ዛፍ እንጅ ሌላ ምግብ የላቸውም፡፡
- 7. የማያሰባ ከረኃብም የማያብቃቃ ከኾነው፡፡
- 8. ፊቶች በዚያ ቀን ተቀማጣዮች ናቸው፡፡
- 9. ለሥራቸው ተደሳቾች ናቸው፡፡
- 10. በከፍተኛ ገነት ውስጥ ናቸው፡፡