84. سورة الإنشقاق - ቁርዓን
- 1. ሰማይ በተቀደደች ጊዜ፤
- 2. ለጌታዋም (ትዕዛዝ) በሰማች ጊዜ፤ (ልትሰማ) ተገባትም፤
- 3. ምድርም በተለጠጠች ጊዜ፤
- 4. በውስጧ ያለውንም ሁሉ በጣለችና ባዶ በኾነች ጊዜ፤
- 5. ለጌታዋም በሰማች ጊዜ፤ (መስማት) ተገባትም፤ (ሰው ሁሉ ሥራውን ይገናኛል)፡፡
- 6. አንተ ሰው ሆይ! አንተ ጌታህን (በሞት) እስከምትገናኝ ድረስ ልፋትን ለፊ ነህ፤ ተገናኚውም ነህ፡፡
- 7. መጽሐፉን በቀኙ የተሰጠ ሰውማ፤
- 8. በእርግጥ ቀላልን ምርመራ ይመረመራል፡፡
- 9. ወደ ቤተሰቦቹም ተደሳች ኾኖ ይመለሳል፡፡
- 10. መጽሐፉን በጀርባው ኋላ የተሰጠ ሰውማ፤