80. سورة عبس - ቁርዓን
- 1. ፊቱን አጨፈገገ፤ ዞረም፡፡
- 2. ዕውሩ ስለ መጣው፡፡
- 3. ምን ያሳውቅሃል? (ከኀጢአቶቹ) ሊጥራራ ይከጀላል፡፡
- 4. ወይም ሊገሠጽ ግሠጼይቱም ልትጠቅመው (ይከጀላል)፡፡
- 5. የተብቃቃው ሰውማ፤
- 6. አንተ ለእርሱ (ለእምነቱ በመጓጓት) በፈገግታ ትቀበለዋለህ፡፡
- 7. ባይጥራራ (ባያምን) ባንተ ላይ ምንም የሌለብህ ስትኾን፡፡
- 8. እየገሰገሰ የመጣህ ሰውማ፤
- 9. እርሱ (አላህን) የሚፈራ ሲኾን፤
- 10. አንተ ከእርሱ ትዝዘናጋለህ፡፡