82. سورة الإنفطار - ቁርዓን
- 1. ሰማይ በተሰነጠቀች ጊዜ፤
- 2. ከዋክብትም ተበታትነው በወደቁ ጊዜ፤
- 3. ባሕሮችም በተከፈቱና በተደበላለቁ ጊዜ፤
- 4. መቃብሮችም በተገለባበጡና (ሙታን) በተነሱ ጊዜ፤
- 5. ማንኛይቱም ነፍስ ያስቀደመችውንና ያቆየችውን ታውቃለች፡፡
- 6. አንተ ሰው ሆይ! በቸሩ ጌታህ ምን አታለለህ?
- 7. በዚያ በፈጠረህ አካለ ሙሉም ባደረገህ ባስተካከለህም፡፡
- 8. በማንኛውም በሻው ቅርፅ በገጣጠመህ (ጌታህ ምን አታለለህ)፡፡
- 9. ተከልከሉ፤ በእውነቱ በፍርዱ ቀን ታስተባብላላችሁ፡፡
- 10. በእናንተ ላይ ተጠባባቂዎች ያሉባችሁ፤ ስትኾኑ፤
- 11. የተከበሩ ጸሐፊዎች የኾኑ፤ (ተጠባባቂዎች)፡፡
- 12. የምትሠሩትን ሁሉ የሚያውቁ፡፡
- 13. እውነተኞቹ ምእምናን በእርግጥ በገነት ውስጥ ናቸው፡፡
- 14. ከሓዲዎቹም በእርግጥ በገሀነም ውስጥ ናቸው፡፡
- 15. በፍርዱ ቀን ይገቧታል፡፡
- 16. እነርሱም ከርሷ ራቂዎች አይደሉም፡፡
- 17. የፍርድ ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?
- 18. ከዚያም የፍርዱ ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?
- 19. (እርሱ) ማንኛይቱም ነፍስ ለሌላይቱ ነፍስ ምንም ማድረግን የማትችልበት ቀን ነው፡፡ ነገሩም ሁሉ በዚያ ቀን ለአላህ ብቻ ነው፡፡