75. سورة القيامة - ቁርዓን
- 1. (ነገሩ ከሓዲዎች እንደሚሉት) አይደለም፡፡ በትንሣኤ ቀን እምላለሁ፡፡
- 2. (ራሷን) ወቃሽ በኾነች ነፍስም እምላለሁ፡፡ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡
- 3. ሰው አጥንቶቹን አለመሰብሰባችንን ያስባልን?
- 4. አይደለም ጣቶቹን (ፊት እንደ ነበሩ) በማስተካከል ላይ ቻዮች ስንኾን (እንሰበስባቸዋለን)፡፡
- 5. ይልቁንም ሰው በፊቱ ባለው ነገር (በትንሣኤ) ሊያስተባብል ይፈልጋል፡፡
- 6. «የትንሣኤው ቀን መቼ ነው?» ሲል ይጠይቃል፡፡
- 7. ዓይንም በዋለለ ጊዜ፡፡
- 8. ጨረቃም በጨለመ ጊዜ፡፡
- 9. ፀሐይና ጨረቃም በተሰበሰቡ ጊዜ፡፡
- 10. «ሰው በዚያ ቀን መሸሻው የት ነው?» ይላል፡፡