79. سورة النازعات - ቁርዓን
- 1. በኃይል አውጪዎች በኾኑት፤
- 2. በቀስታ መምዘዝንም መዘዦች በኾኑት፤
- 3. መዋኘትም ዋኚዎች በኾኑት፤
- 4. መቅደምንም ቀዳሚዎች በኾኑት፤
- 5. ነገርንም አስተናባሪዎች በኾኑት (መላእክት) እምላለሁ፡፡ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡
- 6. ተርገፍጋፊይቱ (ምድር) በምትርገፈገፍበት ቀን፤
- 7. ለጣቂይቱ የምትከተላት ስትኾን (ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡
- 8. በዚያ ቀን ልቦች ተሸባሪዎች ናቸው፡፡
- 9. ዓይኖቻቸው ተዋራጆች (አቀርቃሪዎች) ናቸው፡፡
- 10. «እኛ ወደ መጀመሪያይቱ ኹነታ ተመላሾች ነን?» ይላሉ፡፡