HARUN YAHYA
logo
HARUN YAHYA

  • ሁሉም ስራዎች
  • መጽሐፍት።
  • መጣጥፎች
  • ቪዲዮዎች
  • ስዕሎች
  • ኦዲዮዎች
  • ጥቅሶች
  • ሌላ

ይሰራል
መጽሐፍት።መጣጥፎችቪዲዮዎችስዕሎችኦዲዮዎችጥቅሶችሌላ
ርዕሶች
Harun Yahya © 2025
Harun Yahya © 2025
  1. ዋና ገጽ
  2. ቁርዓን
  3. 26. سورة الشعراء
  • 1. ጠ.ሰ.መ. (ጧ ሲን ሚም)፡፡
  • 2. ይህች ግልጽ ከኾነው መጽሐፍ አንቀጾች ናት፡፡
  • 3. አማኞች ባለመኾናቸው፤ (በቁጭት) ነፍስህን ገዳይ መኾን ይፈራልሃል፡፡
  • 4. ብንሻ በእነሱ ላይ ከሰማይ ተዓምረን እናወርድና አንገቶቻቸው (መሪዎቻቸው) ለእርሷ ተዋራጆች ይኾናሉ፡፡
  • 5. ከአልረሕማንም ዘንድ ኣዲስ የተወረደ ቁርኣን አይመጣላቸውም፤ ከእርሱ የሚሸሹ ቢኾኑ እንጂ፡፡
  • 6. በእርግጥም አስተባበሉ፡፡ የዚያም በእርሱ ይሳለቁበት የነበሩት ወሬዎች (ፍጻሜ) ይመጣባቸዋል፡፡
  • 7. ወደ ምድርም በውስጧ ከመልካም (በቃይ) ጎሳ ሁሉ ብዙን እንዳበቀልን አላዩምን፡፡
  • 8. በዚህ አስደናቂ ምልክት አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡
  • 9. ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊ አዛኝ ነው፡፡
ሼር ያድርጉ
logo
logo
logo
logo
logo
  • 1.ورَةُ الْفَاتِحَة
  • 2.ورَةُ البقرة
  • 3.سُورَةُ آل عمران
  • 4.سورة النساء
  • 5.سورۃ المائدة
  • 6.سورة الأنعام
  • 7.سورة الاعراف
  • 8.سورۃ الانفال
  • 9.سورة التوبة
  • 10.سورة يونس
  • 11.سورۃ ھود
  • 12.سورة يوسف
  • 13.سورة الرعد
  • 14.سورة ابراهيم
  • 15.سورة الحجر
  • 16.سورة النحل
  • 17.سورة الإسراء
  • 18.سورة الكهف
  • 19.سورة مريم
  • 20.سورة طه
  • 21.سورة الأنبياء
  • 22.سورة الحج
  • 23.سورة المؤمنون
  • 24.سورة النور
  • 25.سورة الفرقان
  • 26.سورة الشعراء
  • 27.سورة النمل
  • 28.سورة القصص
  • 29.سورة العنكبوت
  • 30.سورة الروم
  • 31.سورة لقمان
  • 32.سورة السجدة
  • 33.سورة الأحزاب
  • 34.سورة سبإ
  • 35.سورة فاطر
  • 36.سورةيس
  • 37.سورة الصافات
  • 38.سورة ص
  • 39.سورة الزمر
  • 40.سورة غافر
  • 41.سورة فصلت
  • 42.سورة الشورى
  • 43.سورة الزخرف
  • 44.سورة الدخان
  • 45.سورة الجاثية
  • 46.سورة الأحقاف
  • 47.سورة محمد
  • 48.سورة الفتح
  • 49.ورة الحجرات
  • 50.سورة ق
  • 51.سورة الذاريات
  • 52.سورة الطور
  • 53.سورة النجم
  • 54.سورة القمر
  • 55.سورة الرحمن
  • 56.سورة الواقعة
  • 57.سورة الحديد
  • 58.سورة المجادلة
  • 59.سورة الحشر
  • 60.سورة الممتحنة
  • 61.سورة الصف
  • 62.سورة الجمعة
  • 63.سورة المنافقون
  • 64.سورة التغابن
  • 65.سورة الطلاق
  • 66.سورة التحريم
  • 67.سورة الملك
  • 68.سورة القلم
  • 69.سورة الحاقة
  • 70.سورة المعارج
  • 71.سورة نوح
  • 72.سورة الجن
  • 73.سورة المزمل
  • 74.سورة المدثر
  • 75.سورة القيامة
  • 76.سورة الانسان
  • 77.سورة المرسلات
  • 78.سورة النبإ
  • 79.سورة النازعات
  • 80.سورة عبس
  • 81.سورة التكوير
  • 82.سورة الإنفطار
  • 83.سورة المطففين
  • 84.سورة الإنشقاق
  • 85.سورة البروج
  • 86.سورة الطارق
  • 87.سورة الأعلى
  • 88.سورة الغاشية
  • 89.سورة الفجر
  • 90.سورة البلد
  • 91.سورة الشمس
  • 92.سورة الليل
  • 93.سورة الضحى
  • 94.سورة الشرح
  • 95.سورة التين
  • 96.سورة العلق
  • 97.سورة القدر
  • 98.سورة البينة
  • 99.سورة الزلزلة
  • 100.سورة العاديات
  • 101.سورة القارعة
  • 102.Aسورة التكاثر
  • 103.سورة العصر
  • 104.سورة الهمزة
  • 105.سورة الفيل
  • 106.سورة قريش
  • 107.سورة الماعون
  • 108.سورة الكوثر
  • 109.سورة الكافرون
  • 110.سورة النصر
  • 111.سورة المسد
  • 112.سورة الإخلاص
  • 113.سورة الفلق
  • 114.سورة الناس
  • 10. ጌታህም ሙሳን «ወደ በደለኞቹ ሕዝቦች ኺድ» በማለት በጠራው ጊዜ (አስታውስ)፡፡
  • 11. «ወደ ፈርዖን ሕዝቦች (ኺድ) አላህን አይፈሩምን» (አለው)፡፡
  • 12. (ሙሳም) አለ «ጌታዬ ሆይ! እኔ ሊያስተባብሉኝ እፈራለሁ፡፡
  • 13. «ልቤም ይጠብባል፡፡ ምላሴም አይፈታም፡፡ ስለዚህ ወደ ሃሩን ላክ፡፡
  • 14. «ለእነርሱም በእኔ ላይ (የደም) ወንጀል አልለ፡፡ ስለዚህ እንዳይገድሉኝ እፈራለሁ፡፡»
  • 15. (አላህ) አለ «ተው! (አይነኩህም)፡፡ በተዓምራቶቻችንም ኺዱ፡፡ እኛ ከእናንተ ጋር ሰሚዎች ነንና፡፡
  • 16. «ወደ ፈርዖንም ኺዱ፡፡ በሉትም፡- እኛ የዓለማት ጌታ መልክተኞች ነን፡፡
  • 17. «የእስራኤልን ልጆች ከእኛ ጋር ልቀቅ፡፡»
  • 18. (ፈርዖንም) አለ «ልጅ ኾነህ በእኛ ውስጥ አላሳደግንህምን በእኛ ውስጥም ከዕድሜህ ብዙ ዓመታትን አልተቀመጥክምን
  • 19. «ያችንም የሠራሃትን ሥራህን አልሠራህምን አንተም ከውለታ ቢሶቹ ነህ» (አለ)፡፡
  • 20. (ሙሳም) አለ «ያን ጊዜ እኔም ከተሳሳቱት ኾኜ ሠራኋት፡፡
  • 21. «በፈራኋችሁም ጊዜ ከእንናተ ሸሸሁ፡፡ ጌታየም ለእኔ ጥበብን ሰጠኝ፡፡ ከመልክተኞቹም አደረገኝ፡፡
  • 22. «ይህችም የእስራኤልን ልጆች ባሪያ በማድረግህ በእኔ ላይ የምትመጻደቅባት ጸጋ ነት፡፡»
  • 23. ፈርዖን አለ «(ላከኝ የምትለው) የዓለማትም ጌታ ምንድነው»
  • 24. (ሙሳ) «የሰማያትና የምድር በመካከላቸውም ያለው ሁሉ ጌታ ነው፡፡ የምታረጋግጡ ብትኾኑ (ነገሩ ይህ ነው)፤» አለው፡፡
  • 25. (ፈርዖንም) በዙሪያው ላሉት ሰዎች «አትሰሙምን» አለ፡፡
  • 26. (ሙሳ) «ጌታችሁና የመጀመሪያዎቹ አባቶቻችሁም ጌታ ነው» አለው፡፡
  • 27. (ፈርዖን) «ያ ወደእናንተ የተላከው መልክተኛችሁ በእርግጥ ዕብድ ነው» አለ፡፡
  • 28. (ሙሳ) «የምሥራቅና የምዕራብ በመካከላቸውም ያለው ነገር ሁሉ ጌታ ነው፡፡ ታውቁ እንደኾናችሁ (እመኑበት)» አለው፡፡
  • 29. (ፈርዖን) «ከእኔ ሌላ አምላክን ብትይዝ በውነቱ ከእስረኞቹ አደርግሃለሁ» አለ፡፡
  • 30. (ሙሳ) «በግልጽ አስረጅ ብመጣህም እንኳ» አለው፡፡
  • 31. «እንግዲያውስ ከእውነተኞች እንደኾንክ (አስረጁን) አምጣው» አለ፡፡
  • 32. በትሩንም ጣለ፡፡ እርሷም ወዲያውኑ ግልጽ እባብ ኾነች፡፡
  • 33. እጁንም አወጣ፡፡ ወዲያውም እርሷ ለተመልካቾች (የምታበራ) ነጭ ኾነች፡፡
  • 34. (ፈርዖን) በዙሪያው ላሉት መማክርት «ይህ በእርግጥ ዐዋቂ ድግምተኛ ነው» አለ፡፡
  • 35. «ከምድራችሁ በድግምቱ ሊያወጣችሁ ይፈልጋልና ምንን ታዛላችሁ» (አላቸው)፡፡
  • 36. አሉት «እርሱን ወንድሙንም አቆይና በየከተሞቹ ሰብሳቢዎችን ላክ፡፡
  • 37. «በጣም ዐዋቂ ድግምተኞችን ሁሉ ያመጡልሃልና፡፡»
  • 38. ድግምተኞቹም በታወቀ ቀን ቀጠሮ ተሰበሰቡ፡፡
  • 39. ለሰዎቹም «እናንተ ተሰብስባችኋልን» ተባለ፡፡
  • 40. «ድግምተኞቹን እነሱ አሸናፊዎች ቢኾኑ እንከተል ዘንድ» (ተባለ)፡፡
  • 41. «ድግምተኞቹም በመጡ ጊዜ ለፈርዖን እኛ አሸናፊዎች ብንሆን ለእኛ በእርግጥ ዋጋ አለን» አሉት፡፡
  • 42. «አዎን፤ እናንተም ያን ጊዜ ከባለሟሎቹ ትኾናላችሁ» አላቸው፡፡
  • 43. ሙሳ «ለእነርሱ እናንተ የምትጥሉትን ጣሉ» አላቸው፡፡
  • 44. ገመዶቻቸውንና በትሮቻቸውንም ጣሉ፡፡ «በፈርዖንም ክብር ይኹንብን፡፡ እኛ በእርግጥ አሸናፊዎቹ እኛ ነን» አሉ፡፡
  • 45. ሙሳም በትሩን ጣለ፡፡ ወዲያውም እርሷ የሚያስመስሉትን ሁሉ ትውጣለች፡፡
  • 46. ድግምተኞቹም ሰጋጆች ኾነው ወደቁ፡፡
  • 47. (እነሱም) አሉ «በዓለማት ጌታ አመንን፡፡
  • 48. «በሙሳና በሃሩን ጌታ፡፡»
  • 49. (ፈርዖንም) «ለእናንተ ሳልፈቅድላችሁ በፊት ለእርሱ አመናችሁን እርሱ ያ ድግምትን ያስተማራችሁ ታላቃችሁ ነው፡፡ ወደፊትም (የሚያገኛችሁን) በእርግጥ ታውቃላችሁ፡፡ እጆቻችሁንና እግሮቻችሁን (ቀኝና ግራን) በማናጋት እቆረርጣለሁ፡፡ ሁላችሁንም እሰቅላችኋለሁም» አለ፡፡
  • 50. (እነርሱም) አሉ «ጉዳት የለብንም፡፡ እኛ ወደ ጌታችን ተመላሾች ነን፡፡
  • 51. «እኛ የምእምናን መጀመሪያ በመኾናችን ጌታችን ኀጢአቶቻችንን ለእኛ ሊምር እንከጅላለን፡፡»
  • 52. ወደ ሙሳም «ባሮቼን ይዘህ ሌሊት ኺድ፡፡ እናንተ የሚከተሉዋችሁ ናችሁና» ስንል ላክን፡፡
  • 53. ፈርዖንም በየከተሞቹ ሰብሳቢዎችን (እንዲህ ሲል) ላከ፡፡
  • 54. «እነዚህ ጥቂቶች ጭፈሮች ናቸው፡፡
  • 55. «እነርሱም ለእኛ አስቆጪዎች ናቸው፡፡
  • 56. «እኛም ብዙዎች ጥንቁቆች ነን፤» (አለ)፡፡
  • 57. አወጣናቸውም፡፡ ከአትክልቶችና ከምንጮች፡፡
  • 58. ከድልቦችም ከመልካም መቀመጫዎችም፡፡
  • 59. እንደዚሁ ለእስራኤል ልጆች አወረስናትም፡፡
  • 60. ፀሐይዋ ስትወጣም ተከተሉዋቸው፡፡
  • 61. ሁለቱ ጭፍሮችም በተያዩ ጊዜ የሙሳ ጓዶች «እኛ(የፈርዖን ሰዎች) የሚደርሱብን ነን» አሉ፡፡
  • 62. (ሙሳ) «ተዉዉ! ጌታዬ ከእኔ ጋር ነው፡፡ በእርግጥ ይመራኛል» አለ፡፡
  • 63. ወደ ሙሳም «ባሕሩን በበትርህ ምታው» ስንል ላክንበት፡፡ (መታውና) ተከፈለም፡፡ ክፍሉም ሁሉ እንደ ታላቅ ጋራ ኾነ፡፡
  • 64. እዚያም ዘንድ ሌሎችን አቀረብን፡፡
  • 65. ሙሳንም ከእርሱ ገር ያሉትንም ሰዎች ሁሉንም አዳን፡፡
  • 66. ከዚያም ሌሎቹን አሰጠምን፡፡
  • 67. በዚህ ውስጥ ታላቅ ታምር አለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡
  • 68. ጌታህም እርሱ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
  • 69. በእነሱም (በሕዝቦችህ) ላይ የኢብራሂምን ወሬ አንብብላቸው፡፡
  • 70. ለአባቱና ለሕዝቦቹ «ምንን ትግገዛላችሁ» ባለ ጊዜ፡፡
  • 71. «ጣዖታትን እንገዛለን፤ እርሷንም በመገዛት ላይ እንቆያለን» አሉ፡፡
  • 72. (እርሱም) አለ «በጠራችኋቸው ጊዜ ይሰሟችኋልን
  • 73. «ወይስ ይጠቅሟችኋልን ወይስ ይጎዷችኋልን»
  • 74. «የለም! አባቶቻችን እንደዚሁ ሲሠሩ አገኘን» አሉት፡፡
  • 75. «ትግገዙት የነበራችሁትን አስተዋላችሁን
  • 76. «እናንተም የቀድሞዎቹ አባቶቻችሁም (የተግገዛችሁትን)፡፡»
  • 77. «እነሱም (ጣዖቶቹ) ለእኔ ጠላቶች ናቸው፡፡ ግን የዓለማት ጌታ ሲቀር (እርሱ ወዳጄ ነው)፡፡
  • 78. «(እርሱ) ያ የፈጠረኝ ነው፡፡ እርሱም ይመራኛል፡፡
  • 79. «ያም እርሱ የሚያበላኝና የሚያጠጣኝ ነው፡፡
  • 80. «በታመምኩም ጊዜ እርሱ ያሽረኛል፡፡
  • 81. «ያም የሚገድለኝ ከዚያም ሕያው የሚያደርገኝ ነው፡፡
  • 82. ያም በፍርዱ ቀን ኀጢአቴን ለእኔ ሊምር የምከጅለው ነው፡፡
  • 83. ጌታዬ ሆይ! ዕውቀትን ስጠኝ! በደጋጎቹም ሰዎች አስጠጋኝ፡፡
  • 84. በኋለኞቹም ሕዝቦች ውስጥ ለእኔ መልካም ዝናን አድርግልኝ፡፡
  • 85. የጸጋይቱን ገነት ከሚወርሱትም አድርገኝ፡፡
  • 86. ለአባቴም ማር፡፡ እርሱ ከተሳሳቱት ነበረና፡፡
  • 87. በሚቀሰቀሱበት ቀንም አታዋርደኝ፡፡
  • 88. ገንዘብም ልጆችም በማይጠቅሙበት ቀን፡፡
  • 89. ወደ አላህ በንጹህ ልብ የመጣ ሰው ቢኾን እንጅ፡፡»
  • 90. ገነትም ለፈሪዎች በምትቀረብበት (ቀን)፡፡
  • 91. ገሀነምም ለጠመሞች በምትገለጽበት (ቀን)፡፡
  • 92. ለእነሱም በሚባል ቀን «ትግገዟቸው የነበራችሁት የት ናቸው»
  • 93. «ከአላህ ሌላ ሲኾኑ ይረዱዋችኋልን ወይስ (ለራሳቸው) ይርረዳሉን»
  • 94. በውስጧም እነሱና ጠማሞቹ በፊቶቻቸው ተጥለው ይንከባለላሉ፡፡
  • 95. የሰይጣንም ሰራዊቶች መላውም (ይጣላሉ)፡፡
  • 96. እነርሱም በእርሷ ውስጥ የሚከራከሩ ኾነው ይላሉ፡-
  • 97. በአላህ እንምላለን፤ እኛ በግልጽ መሳሳት ውስጥ ነበርን፡፡
  • 98. (ጣዖቶቹን) በዓለማት ጌታ ባስተካከልናችሁ ጊዜ፡፡
  • 99. አመጸኞቹም እንጅ ሌላ አላሳሳተንም፡፡
  • 100. ከአማላጆችም ለእኛ ምንም የለንም፡፡
  • 101. አዛኝ ወዳጂም (የለንም)፡፡
  • 102. ለእኛም አንዲት ጊዜ መመለስ በኖረችንና ከአማኞቹ በኾን እንመኛለን (ይላሉ)፡፡
  • 103. በዚህ ውስጥ አስደናቂ ግሳጼ አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡
  • 104. ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
  • 105. የኑሕ ሕዝቦች መልክተኞችን አስተባበሉ፡፡
  • 106. ወንድማቸው ኑሕ ለእነሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን
  • 107. «እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
  • 108. «አላህንም ፍሩ ታዘዙኝም፡፡
  • 109. «በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልጠይቃችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
  • 110. «አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡»
  • 111. (እነርሱም) «ወራዶቹ የተከተሉህ ኾነህ ለአንተ እናምናለን» አሉት፡፡
  • 112. (እርሱም) አላቸው «ይሠሩት በነበሩት ነገር ምን ዕውቀት አለኝ፡፡
  • 113. «ምርመራቸው በጌታዬ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡ ብታውቁ ኖሮ (ይህንን ትርረዱ ነበር)፡፡
  • 114. «እኔም አማኞችን አባራሪ አይደለሁም፡፡
  • 115. «እኔ ግልጽ አስፈራሪ እንጅ ሌላ አይደለሁም፡፡»
  • 116. «ኑሕ ሆይ! (ከምትለው) ባትከለከል በእርግጥ ከሚወገሩት ትኾናለህ» አሉት፡፡
  • 117. (እርሱም) አለ «ጌታዬ ሆይ! ሕዝቦቼ አስተባበሉኝ፡፡
  • 118. «በእኔና በእነርሱም መካከል (ተገቢ) ፍርድን ፍረድ፡፡ አድነኝም፡፡ ከእኔ ጋር ያሉትንም ምእምናን፡፡»
  • 119. እርሱንም ከእርሱ ጋር ያለውንም ሁሉ በተመላው መርከብ ውስጥ አዳን፡፡
  • 120. ከዚያም በኋላ ቀሪዎቹን አሰጠምን፡፡
  • 121. በዚህ ውስጥ ታላቅ ግሳጼ አለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡
  • 122. ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
  • 123. ዓድ መልክተኞችን አስተባበለች፡፡
  • 124. ወንድማቸው ሁድ ለነርሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን
  • 125. «እኔ ለናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
  • 126. «አላህንም ፍሩ ታዘዙኝም፡፡
  • 127. «በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አለምናችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
  • 128. «የምትጫወቱ ኾናችሁ በከፍተኛ ስፍራ ሁሉ ላይ ምልክትን ትገነባላችሁን
  • 129. «የውሃ ማጠራቀሚያዎችንና ሕንፃዎችንም ዘላለም መኖርን የምትከጅሉ ኾናችሁ ትሠራላችሁን
  • 130. «በቀጣችሁም ጊዜ ጨካኞች ኾናችሁ ትቀጣላችሁን
  • 131. «አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡
  • 132. «ያንንም በምታውቁት (ጸጋ) ያጣቀማችሁን ፍሩ፡፡
  • 133. «በእንስሳዎችና በልጆች ያጣቀማችሁን፡፡
  • 134. «በአትክልቶችና በምንጮችም፡፡
  • 135. «እኔ በእናንተ ላይ የታላቅን ቀን ቅጣት እፈራለሁና፡፡»
  • 136. (እነርሱም) አሉ «ብትገስጽም ወይም ከገሳጮቹ ባትኾንም በእኛ ላይ እኩል ነው፤ (ያለንበትን አንለቅም)፡፡
  • 137. «ይህ የፊተኞቹ ሰዎች ፀባይ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
  • 138. «እኛም የምንቅቀጣ አይደለንም» (አሉ)፡፡
  • 139. አስተባበሉትም፡፡ አጠፋናቸውም፡፡ በዚህም ውስጥ እርግጠኛ ግሳጼ አለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእመናን አልነበሩም፡፡
  • 140. ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
  • 141. ሰሙድ መልክተኞችን አስተባበለች፡፡
  • 142. ወንድማቸው ሷሊህ ለእነርሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን
  • 143. «እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
  • 144. «አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡
  • 145. «በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልለምናችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
  • 146. «በዚያ እዚህ ባለው (ጸጋ) ውስጥ የረካችሁ ኾናችሁ ትተዋላችሁን
  • 147. «በአትክልቶችና በምንጮች ውስጥ፡፡
  • 148. «በአዝመራዎችም ፍሬዋ የበሰለ በኾነች ዘንባባም፤ (ውስጥ ትተዋላችሁን)
  • 149. «ብልሆች ኾናችሁ ከጋራዎች ቤቶችንም ትጠርባላችሁ፡፡
  • 150. «አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡
  • 151. «የወሰን አላፊዎችንም ትዕዛዝ አትከተሉ፡፡
  • 152. «የእነዚያን በምድር ላይ የሚያጠፉትንና የማያበጁትን፡፡»
  • 153. (እነሱም) አሉ «አንተ በብዙ ከተደገመባቸው ሰዎች ብቻ ነህ፡፡
  • 154. «አንተ ብጤያችን ሰው እንጅ ሌላ አይደለህም፡፡ ከእውነተኞቹም እንደኾንክ ተዓምርን አምጣ፡፡»
  • 155. (እርሱም) አለ «ይህች ግመል ናት፡፡ ለእርሷ የመጠጥ ፋንታ አላት፡፡ ለእናንተም የታወቀ ቀን ፋንታ አላችሁ፡፡
  • 156. «በክፉም አትንኳት፡፡ የታላቅ ቀን ቅጣት ይይዛችኋልና፡፡»
  • 157. ወጓትም፡፡ ወዲያውም ተጸጻቾች ኾነው አነጉ፡፡
  • 158. ቅጣቱም ያዛቸው፡፡ በዚህም ውስጥ ግሳፄ አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእመናን አልነበሩም፡፡
  • 159. ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
  • 160. የሉጥ ሕዝቦች መልክተኞችን አስተባባሉ፡፡
  • 161. ወንድማቸው ሉጥ ለእነርሱ ባለ ጊዜ «አትጠነቀቁምን
  • 162. «እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
  • 163. «አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡
  • 164. «በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልለምናችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
  • 165. «ከዓለማት ሰዎች ወንዶችን ትመጣላችሁን
  • 166. «ከሚስቶቻችሁም ጌታችሁ ለናንተ የፈጠረላችሁን ትተዋላችሁን በእውነቱ እናንተ ወሰን አላፊዎች ሕዝቦ ናችሁ፡፡»
  • 167. (እነርሱም) አሉ «ሉጥ ሆይ! ባትከለከል በእርግጥ (ከአገር) ከሚወጡት ትኾናለህ፡፡»
  • 168. (እርሱም) አለ «እኔ ሥራችሁን ከሚጠሉት ሰዎች ነኝ፡፡
  • 169. «ጌታዬ ሆይ! እኔንም ቤተሰቦቼንም ከሚሠሩት ሥራ (ቅጣት) አድነን፡፡»
  • 170. እርሱንም ቤተሰቦቹንም በጠቅላላ አዳንናቸው፡፡
  • 171. በቀሪዎቹ ውስጥ የኾነች አሮጊት ብቻ ስትቀር (እርሷ ጠፋች)፡፡
  • 172. ከዚያም ሌሎቹን አጠፋን፡፡
  • 173. በእነሱም ላይ (የድንጋይን) ዝናምን አዘነምንባቸው፡፡ የተስፈራሪዎቹም ዝናም (ምንኛ) ከፋ፡፡
  • 174. በዚህ ውስጥ አስደናቂ ተዓምር አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእመናን አልነበሩም፡፡
  • 175. ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
  • 176. የአይከት ሰዎች መልክተኞችን አስተባበሉ፤
  • 177. ሹዕይብ ለእነርሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን
  • 178. «እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
  • 179. «አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡
  • 180. «በርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልጠይቃችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
  • 181. «ስፍርን ሙሉ፡፡ ከአጉዳዮቹም አትኹኑ፡፡
  • 182. «በትክክለኛ ሚዛንም መዝኑ፡፡
  • 183. «ሰዎችንም ነገሮቻቸውን አታጉድሉባቸው፡፡ በምድርም ላይ አጥፊዎች ኾናችሁ አታበላሹ፡፡
  • 184. «ያንንም የፈጠራችሁን የቀድሞዎቹንም ፍጡሮች (የፈጠረውን) ፍሩ፡፡»
  • 185. አሉ «አንተ በብዛት ከተደገመባቸው ሰዎች ነህ፡፡
  • 186. «አንተም ብጤያችን ሰው እንጅ ሌላ አይደለህም፡፡ እነሆ ከውሸታሞች ነህ ብለን እንጠረጥርሃለን፡፡
  • 187. «ከእውነተኞቹም እንደኾንክ በእኛ ላይ ከሰማይ ቁራጭን ጣልብን፡፡»
  • 188. «ጌታዬ የምትሠሩትን ሁሉ ዐዋቂ ነው፤» አላቸው፡፡
  • 189. አስተባበሉትም፡፡ የጥላይቷ ቀን ቅጣትም ያዛቸው፡፡ እርሱ የከባድ ቀን ቅጣት ነበርና፡፡
  • 190. በዚህ ውስጥ አስደናቂ ተዓምር አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእምናን አልነበሩም፡፡
  • 191. ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
  • 192. እርሱም (ቁርኣን) በእርግጥ ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው፡፡
  • 193. እርሱን ታማኙ መንፈስ (ጂብሪል) አወረደው፤
  • 194. ከአስፈራሪዎቹ (ነቢያት) ትኾን ዘንድ በልብህ ላይ (አወረደው)፡፡
  • 195. ግልጽ በኾነ ዐረብኛ ቋንቋ፡፡
  • 196. እርሱም (ቁርኣን) በቀድሞዎቹ መጻሐፍት ውስጥ (የተወሳ ነው)፡፡
  • 197. የእስራኤል ልጆች ሊቃውንት የሚያውቁት መኾኑ ለእነርሱ (ለመካ ከሓዲዎች) ምልክት አይኾናቸውምን
  • 198. ከአዕጀሞች ባንዱ ላይ ባወረድነውም ኖሮ፤
  • 199. በእነርሱ ላይ ባነበበውም በእርሱ አማኞች አይኾኑም ነበር፡፡
  • 200. እንደዚሁ (ማስተባበልን) በተንኮለኞች ልቦች ውስጥ አስገባነው፡፡
  • 201. አሳማሚ ቅጣትን እስከሚያዩ ድረስ በእርሱ አያምኑም፡፡
  • 202. እነርሱ የማያውቁ ሲኾኑ (ቅጣቱ) ድንገት እስከሚመጣባቸውም ድረስ (አያምኑም)፡፡
  • 203. (በመጣባቸው ጊዜ) «እኛ የምንቆይ ነን» እስከሚሉም (አያምኑም)፡፡
  • 204. በቅጣታችን ያቻኩላሉን
  • 205. አየህን ብዙ ዓመታትን ብናጣቅማቸው፤
  • 206. ከዚያም ያ ይስፈራሩበት የነበሩት ቢመጣባቸው፤
  • 207. ይጣቀሙበት የነበሩት ሁሉ ከእነሱ ምንም አያብቃቃቸውም፡፡
  • 208. አንዲትንም ከተማ ለእርሷ አስፈራሪዎች ያሏት (እና ያስተባበለች) ኾና እንጅ አላጠፋንም፡፡
  • 209. (ይህች) ግሳፄ ናት፡፡ በዳዮችም አልነበርንም፡፡
  • 210. ሰይጣናትም እርሱን (ቁርኣንን) አላወረዱትም፡፡
  • 211. ለእነርሱም አይገባቸውም፤ አይችሉምም፡፡
  • 212. እነርሱ (የመላእክትን ንግግር) ከመስማት ተከለከሉ ናቸው፡፡
  • 213. ከአላህም ጋር ሌላን አምላክ አትግገዛ፤ ከሚቀጡት ትኾናለህና፡፡
  • 214. ቅርቦች ዘመዶችህንም አስጠንቅቅ፡፡
  • 215. ከምእምናንም ለተከተሉህ ሰዎች ክንፍህን ዝቅ አድርግ፤ (ልዝብ ኹን)፡፡
  • 216. «እንቢ» ቢሉህም «እኔ ከምትሠሩት ንጹሕ ነኝ» በላቸው፡፡
  • 217. አሸናፊ አዛኝ በኾነው (ጌታህ) ላይም ተጠጋ፡፡
  • 218. በዚያ ለሶላት በምትቆም ጊዜ በሚያይህ፡፡
  • 219. በሰጋጆች ውስጥ መዘዋወርህንም (በሚያየው ጌታህ ላይ ተጠጋ)፡፡
  • 220. እነሆ እርሱ ሰሚው ዐዋቂው ነውና፡፡
  • 221. ሰይጣናት በማን ላይ እንደሚወርዱ ልንገራችሁን
  • 222. በውሸታም ኀጢአተኛ ሁሉ ላይ ይወርዳሉ፡፡
  • 223. የሰሙትን (ወደ ጠንቋዮች) ይጥላሉ፡፡ አብዛኞቻቸውም ውሸታሞች ናቸው፡፡
  • 224. ባለ ቅኔዎችንም ጠማማዎቹ ይከተሉዋቸዋል፡፡
  • 225. እነርሱ በ(ንግግር) ሸለቆ ሁሉ የሚዋልሉ መኾናቸውን አታይምን
  • 226. እነሱም የማይሠሩትን ነገር የሚናገሩ መኾናቸውን (አታይምን)፤
  • 227. እነዚያ ያመኑና መልካም ሥራዎችን የሠሩ አላህንም በብዛት ያወሱ ከተበደሉም በኋላ (በቅኔ) የተከላከሉ ሲቀሩ፤ (እነርሱ አይወቀሱም)፡፡ እነዚያም የበደሉ (ከሞቱ በኋላ) እንዴት ያለን መመለስ እንደሚመለሱ በእርግጥ ያውቃሉ፡፡